Saturday, April 28, 2012

እንዲህ ተጀመረ


                                       የእሾሀማው ፍሬ

አዳም እንዲበላ ባታቀብል ኖሮ
እሷም ባታዳምጥ ይህ እንዳይሆን ድሮ
ሄዋኔ ጥናቴ አዳኝ መድሀኒቴ
የጎኔ ስብራት ጠጋኝ ነሽ ህይወቴ
ግና አሁን ገና 
ብነቃ እንደገና 
አንቺንም ባልኮነንኩ
በራሴው መስጠቴን ይናገሩ ነበር የገዛ እጆቼ
ያኔ ታዲያ ምን እል ነበር አግዢኝ ወዳጄ
ተራው በሁላችን አንድ አንድ አይነት ከነበር 
ወቃሽና ተወቃሽ ባንሆን አይሻልም ነበር

 አርአያ መካሻ

No comments:

Post a Comment