Saturday, April 28, 2012

ሲዳማ

ሲዳማ…..


አንዱ ካንዱ ባሻገር
ከጥልፉ ከወንዙ ዳር
ከማደስ ውልደት ጥግ
የባልደራሱ ማደግ
ያንተነትህ ክታብ እውነት
ሁለት ሲሆን ያንተ ውስጠት
ከኮከቡ ሻግራ ከሰማይ ጥቁረት ድምቀት
የብርሀን ፀዳል አይደል የምታየው እውነት                                                  
ሁለትነት በልዩነት ብርሃንህ በጭለማ
የዘመናት ኑረት ትርቀት አይደል ያሳለፍከው ኑሮ ዜማ
ባትደንስ ባትቦርቅ ‘ንኳን
ባታዝንም ባትከፋ ‘ንኳን
ሁለትነት ላንተ አንድ አይደለም
ህይወት ሲዳማ እንጂ ትርቀቱ ሌላውማ የመኖርህ ትርጉም የለም ፡፡



 አርአያ መካሻ/ቺምፑ /ዛሬ1/8/04

No comments:

Post a Comment